መግቢያ | ስለአኛ | አድራሻ

   
 

ትራንስፓረንሲ ኢትዮጵያ መንግስታዊ  ያልሆነ፣ ለትርፍ የማይንቀሳቀስ ሀገር በቀል ድርጅት ነው፡፡ ትራንስፓረንሲ ኢትዮጵያ ሙስና በሀገርና በወገን ላይ የሚያደርሰውን ማኀበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ለመከላከልና ለመቀነስ ተመሳሳይ አለማ ካላቸው ሲቪል ድርጅቶች፣ መንግስታዊ ተቋማት፣ አለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ከግሉ ዘርፍ፣ ከማዲያ አካላትና ከኀብረተሰቡ ጋር ጥምረት ፈጥሮ የሚንቀሳቀስ የፀረ-ሙስና ማኀበር ነው፡፡

ይህ ተቋም መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር ሰፍኖ የህግ የበላይነት የተከበረበት፣ ጠንካራ የሆነ የፀረ-ሙስና ጥምረት የተፈጠረባት በአለም ላይ እንደምሳሌ የምትጠቀስ ኢትዮጵያ ማየት ግቡ ያደረገ ነው፡፡

ትራንስፓረንሲ ኢትዮጵያ ለማቋቋም መነሻ የሆነው የአለም አቀፍን የፀረ-ሙስና እንቅስቀሴ በተለያየ አጋጣሚ በመሳተፍ ከአለም አቀፍ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አመራሮች ጋር ጠንካራ ግኑኝነት መፍጠር በቻሉ ኢትዮጵያውያን አማካኝነት በቀረበ ሀሳብ ነው፡፡

በዚህ መሠረት ማኀበሩን ለመመስረት በተሰባሰቡ ዜጎች እንቅስቃሴ ተጀምሮ ጥር 23 እና 24 ቀን 1995 ዓ.ም በአፍሪካ ኢካኖሚ ኮሚሽን ስብሰባ አዳራሽ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከግል ዘርፍ፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከሠራተኛ ማኀበራት፣ ከትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተወካዮችና ከታዋቂ ግለሰቦች የተወጣጡ ከ 300 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በተለያየ ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ እንዲቀርብና ውይይት እንዲካሄድበት ከተደረገ በኃላ በዚህ ህዝባዊ የፀረ-ሙስና ኮንፍረንስ የማኀበሩን ከፍተኛ አመራር አባላት በመምረጥ በይፋ ማኀበሩን ለመመስረት ተችሏል፡፡

 

 
  Member Login
  Opinion Poll: View Result

Do you think that corruption is a problem in Ethiopia?


 
             View Result
 
  Membership Form

   Download Membership form

Fill Membership Form Online

 
 
  GCR 2008
 
 
Copy right © 2008 Transparency Ethiopia